መጋቢት 5 ዕረፍቱ ለአቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ
ከዚህ ዓለም የሚለይበት በቀረበ ጊዜ እነሆ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እነሆ ተገለጠለት፡፡ ስሙን ለሚጠራና መታሰቢያውንም ለሚያደርግ እስከ ዐሥራ አምስት ትውልድ የምሕረት ቃል ኪዳን ሰጠው፡፡የዕድሜውም ዘመናት አምስት መቶ ስድሳ ሁለት ሲሆን በሰላም በፍቅር ዐረፈ፤ጌታችንም ነፍሱን ተቀበለ፤ አቅፎም ሳማት፤ በመላእክትና በቅዱሳን ሁሉ ምስጋና አሳረጋት፡፡
コメント